ክስተቶች

ውስጥ የፅዳት ዘመቻ

image description
የመጀመሪያ ቀን icon
የመጨረሻ ቀን icon
አካባቢ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ

 

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ እና የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን  በጋራ ለከተማ አስተዳደሩ አመራሮች እንዲሁም ለቢሮው እና ለኮርፖሬሽኑ የእስልምና እምነት ተከታይ ሰራተኞች ደማቅ የኢፍጣር መርሀ ግብር ዛሬ አካሂደዋል።

የረመዳን ወር  የአብሮነት ፣ የወንድማማችነት እና የመተሳሰብ  አስተምህሮ የሚገለጽበት መሆኑን ምክንያት በማድረግ ነው የኢፍጣር መርሀ ግብሩ የተካሄደው።

የቤቶች ልማት እና አስተዳደር  ቢሮ ኃላፊ ክብርት ቅድስት ወ/ጊዮርጊስ እና  ክቡር አቶ ሽመልስ ታምራት የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር  እንዲሁም የቢሮው እና የኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ አመራሮች በመርሀ ግብሩ ላይ ለተገኙት  እንግዶች አቀባበል አድርገዋል።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ ለረመዳን የፆም ወር እና ከፊታችን ለሚከበረው ለ1ሺ 446ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል ከወዲሁ እንኳን አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውንም ገልፀዋል።

በረመዳን የፆም ወር የመጨረሻው አርብ በሆነው በዚህ ደማቅ የኢፍጣር መርሀ ግብር ላይ የከተማ አስተዳደሩ  አመራሮች እንዲሁም የቢሮው እና የኮርፖሬሽኑ የእስልምና እምነት ተከታይ ሰራተኞች  ታድመዋል ።

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aahdab

  • icon 9:30am - 1:00pm
  • የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ

ተዛማች ኁነቶች